የበላልበልሃን ብሎግ delete ማድረግ ተከትሎ በዛ ላይ ወጥተው የነበሩትን ጽሁፎች በዚህ ብሎግ ላይ በድጋሚ እንማወጣ ባስታወቁት መሰረት እነሆ አንድ የጠበቃ ቀልድ፡፡
አንድ ጠበቃዎችን በመኪና በመግጨት ራሱን የሚያዝናና የከባድ መኪና ሾፌር ነበር፡፡ ሁሌ በመንገድ ላይ ጠበቃ ሲያይ መኪናውን ያጠመዘዝና ያለርህራሄ ጠበቃውን ከገጨው በኋላ ‘ድው!’ የሚል የግጭት ድምጽ ሲሰማ አንጀቱ ይርሳል፡፡ አንድ ቀን መኪናውን እየነዳ ወደ ስራ ሲሄድ አንድ ቄስ መንገድ ዳር ቆመው ሲያይ ‘ዛሬ እንኳን ደግ ልስራ !’ ብሎ በማሰብ መኪናውን ያቆምላቸዋል፡፡
‹‹ወዴት ነው የሚሄዱት አባት?” ይጠይቃቸዋል፡፡
“ፊት ለፊት ወደአለችው ቤተክርስቲያን ነው ልጄ!” ቄሱ በትህትና መለሱለት፡፡
“ችግር የለም አባት ይግቡ እኔ እወስድዎታለሁ”
በሹፌሩ ደግነት የተደሰቱት ቄስ መኪና ውስጥ ገብተው ጉዞ ይጀምራሉ፡፡ በጉዞአቸው መሐል ሾፌሩ በመንገድ ዳር አንድ ጠበቃ ቦርሳውን ይዞ ሲሄድ ሲያይ ሳያውቀው በደመነፍስ መኪናውን በፍጥነት አዙሮ ወደ ጠበቃው መንዳት ይጀምራል፡፡ ሆኖም ከአጠገቡ የተቀመጡት ቄስ መሆናቸውን ሲያስብ የመኪናውን አቅጣጫ በማስቀየስ ጠበቃውን ለትንሽ ይስተዋል፡፡ ጠበቃው እንዳልተገጫ እርግጠኛ ቢሆንም “ድው!” የሚል ድምጽ ግን ሰምቷል፡፡ በፊት መስታወት ቢመለከትም የተገጨ ጠበቃ አልታየውም፡፡ በነገሩ ግራ የተጋባው ሾፌር “ይቅርታ ያድርጉልኝ አባቴ ያንን ጠበቃ እኮ ለትንሽ ገጭቼው ነበር!” ሲል ለቄሱ ይናዘዛል፡፡
ቄሱም በኩራት መንፈስ “ግድ የለህም ልጄ በበሩ አገጩን ብዬ ደፍቼዋለሁ!”
Filed under: law fun
